ምንም አትበይኝ፣ ስትሄጂ ጥለሺኝ ዝም ብለሽ ሂጂ፣ መሄድሽን ሳትነግሪኝ፤ ከኔጋር ለመሆን፣ ልብሽ ባይፈቅድልሽ መንገዱ ግን ይቅናሽ፣ ክፋም አይግጠምሽ፤ ፍቅርሽን መሸከም፣ ጫንቃዬ ባይችልም ከኔ ጋር ሁኚ፣ ብዬ አላስገዽሽም:: መሳቅ ሲያስፋልገኝ፣ በትዝታ አይሻለሁ ማልቀስ ቢያስፈልገኝ፣ ብቻዬን ቁጭብዬ እነፈርቃለሁ፤ በቃ በቃ ሂጂ፣ ዞር ብለሽ አትይኝ ሆዴን አታባቢው፣ ቻዎም አትበይኝ፤ ድምዕሽን አጥፊና፣ ኮቴሽን ጠብቀሽ ሳታንኮሻኩሺ፣ ውጪ ልቤን ዘግተሽ ቁልፉን ግን አስቀምጪው፣ አደራ ይሁንብሽ፡፡ ታዬ አለሙ 2005 ዓም ትንሽ ማስተካከያ ›› በአኒቲ