Skip to main content

Posts

Showing posts from October, 2012

ሳላሀዲን ሰዓድ ካዋራኝ የተገለበጠ ኢንተርቪው

Invisible journalist asking question through Magnetic Force of the mind First Audition የእምነት ነፃነት መፅሄት የመጀመሪያው እትም በሆነው ቅፅ ፻ የእንግዳችን ፕሮግራም አምድ ላይ ተጋባዥ ያደረግነው የጭንቅ ቀን ደራሹ የብሄራዊ ቡድናችን አጥቂ ከሆነው ሳላሀዲን ሰዒድ ጋር ያደረግነውን አጭር ቆይታ እነሆ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡ የእምነት ነፃነት መፅሄት ፡ ሳላሀዲን መቼም በዚህ አጭር ግዜ ውስጥ (ልምምድ ላይ እንደመሆንህ መጠን) ለቃለ ምልልሱ ፍቃደኛ ሆነህ ስለመጣህ እያመሰገንን በቅድሚያ በአንባቢዎቻችን ስም እንኳን በደህና መጣህ ለማለት እንወዳለን፡፡ ሳላሀዲን ፡ እንኳን ደህና ቆያችሁኝ፣ የመጀመርያ እንግዳም ስላደረጋችሁኝ አመሰግናለሁ፡፡ ጥያቄ ፡ ሙስሊም እንደመሆንህ መጠን የመጅሊስ ምርጫ በቀበሌ መባሉን እንዴት ነበር ያየህው? ሳላሀዲን ፡ በግልምጫ፡፡ ጥያቄ ፡ ለምን? ሳላሀዲን፡ ምክንያቱም ድርጊቱ በመረብ ኳስ ሜዳ ላይ ጎል ተክሎ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያን የመጫወት ያህል ነው፡፡ ጥያቄ፡ የመንግስት አካላት ምርጫው በቀበሌ መሆኑ ህገመንግስቱን አይፃረንም ባዮች ናቸው አንተ ምን ትላለህ? ሳላሀዲን፡ እግር ኳስ ተጫዋች ስለሆንኩ የመረዳት አቅም የለውም በእግር ማሰብ አይደለም እንደማትለኝ እያመንኩ፡፡ ይህ ቀላል ጥያቄ ነው በሚቀጥለው ምርጫ 2007 የመንግስት ተወካይን ለመምረጥ የሀገሪቱ ህዝብ በመስጊድ እና በቤተክርስታን ማከናወን እንደሚችል ቃል ከገቡና በምርጫ ቦርድ ወይም በፓርላማው እንደ አንድ ፖሊሲ ካፀደቁት ምንም ችግር የለውም ባይ ነኝ፡፡ ጥያቄ፡ በሌላ መንገድ እምነት እና ፖለቲካን (ሰርግና ሞት አንድ ነው ጨፍር ምንድነው) እንደሚለው የ...

አንድ ነና

አንተ ረጅም ሎጋ እኔ አጭር ፉንጋ አንተ ሃብታምና አዋቂ እኔ ደሃ ዜጋ ሌቱን የማድር ያለንቅልፍ ቀኑን የምውል ስፈጋ ዓለምን ስትዞር አንተ እረፍት የለም እኔ ጋ አሁን ግን በቅቶኛል ምሬት ካናቴ ወጥቷል የ “አንድ ነን” ዲስኩርህ ሳያንሰኝ ዝምታዬ ጮሆብኛል ሞፈርና ቀንበሬ  እንኳ ድምጽ አውጥተው ወቅሰውኛል ውሸትህን ችዬ  ስኖር አይተው “ደንቆሮ ነህ ወይ” ብለውኛል እናማ ባልንጀሬ ሩቅ ሆነህ  የደለልከኝ እዚህ ኖረህ የራቅከኝ እስቲ ቼክህን አውሰኝ ከመልክህም ትንሽ ቸረኝ ትዳርህም ዛሬ ከኔ ትደር ገላዬን ካልጋህ ላኑር ላሳርፍ የዛለ ወገቤን ልጠግን ስብራቴን አንተ ደግሞ ኑር ኑሮዬን ተረከበኝ ስራዬን “ለምን”ን ምን አመጣው “አንድ ነና” ጓዴ ፈጠራዬም አይደል ያንተው ነው ዘመዴ ክረምት ከበጋ ይህን አይደል የሰበከኝ “ሁለት ነን” ስልህ “አይ አንድ ነን” አይደል ያልክኝ እንግዲህ ድህነቴን ቻለው መከራዬን ተሸከም እኔ ድሎትን ልልመድ ህመሜንም ላሣክም እኔ ልጆቼን ላስተምር አንተ እረኞችን ውለድ እኔ ከቢሮህ ልዋል አንተ ከብቶቼን ማግድ አንተ ቦርዴ ከጓደኞቼ ተጋራ እኔም ከመጠጦችህ ልጎንጭ እየቀዳሁ “ቺርስ” ልበል አንዴ ከቢጫው አንዴ ከቀይ አልያም ከነጭ ኮረዶችን ሰብስቤ ከሳሎንህ እኔ ሺሻ ላቡን አንተ ግባ ከኩሽናዬ በኩበት ጭስ ታጠን ግራሜውን ተው ወንድሜ ይልቅስ አድምጠኝ ላንቺም ጥያቄ አለኝ እህቴ አንዴ ልብ በይኝ ያንተ ከኔ አንድ መሆን የኔን ሽክም ካላዘለ የነም አንቺነቴ ያንቺን ምቾት ካልታደለ አንድነታችን ታዲያ የቱ ጋር ነው ያለ? ግርማ ታደሰ መስከረም 2005

እማማ በላይነሽ

ዛሬ ምነው አኒቲ ወሬ አበዛ እንዳትሉኝ፡፡ መቀባጠር ነው ብላችሁ ከሆነም በዓመት አንዴ እንድቀባጥር ከፈቀዳችሁልኝ እሰየሁ ዝቅ ዝቅ ሳቅ ሳቅ እያላችሁ አብራችሁኝ ዝለቁ፡፡ መቼም በዝህች ዓለም ላይ ስንኖር፤ በዕለት ተዕለት ንሮአችን፣ ማለትም በቤታችን፤ በሰፈራችን፤ በትምህርት ቤት፤ በስራ ቦታ፤ ሌላም ሌላም ቦታዎች የሚያጋጥሙን ከንፈር አስለጣጭ፤ ጥርስ አስከፋች ገጠመኞች ሊኖሩን ግድ ይላል፡፡ እናላችሁ ቀጥዬ የማወጋችሁን ገ ጠመኝ ያካፈለችኝ አንድ የሥራ ባልደረባዬ ስትሆን ግዜው ቢቆይም (ያኔ በየሰፈሩ እና በየ ስራ ስሩ ስለ ኤች.አይቪ ማስተማር ብርቅ በነበረ ወቅት) እኔ የሰማሁት በዚሁ ዓመት በመሆኑ ለራሴ ብቻ ለምን ልገረም ብዬ (ያው መቼም ከናንተ የምደብቀው ነገር የለኝምና) ላካፍላችሁ ወደደኩ፡፡ ቦታው ኦሮሚያ ክልል አንቦ ከተማ አከባቢ ይመስለኛል ባልዘነጋው፡፡ የምላችሁ ወዳጄ ስለ ኤች.አይ.ቪ. ኤድስ እና ስለ ኮንደም ለከተማው ሴት ማህበራት እንድታስተምር ትጋበዝና ወደ ስፍራው ታቀናለች፡፡ ትምህርቱ ተጀመረ ተሳታፊወቹ ሴቶች ሲሆኑ ያው መሪ መኖሩ አይቀርምና በመሀላቸው የተለያዩ ተሰሚነት ያላቸው የየእድር መሪዎች ይገኙበታል፡፡ ከነኚህም ሴት መሪዎች መካከል ይህን ፅሁፍ ለመፃፍ ያበቁን እማማ በላይነሽ ይገኙበታል፡፡ እማማ በላይነሽ በከተማው የእድር መሪ ብቻም ሳይሆኑ ተሰሚነት ካላቸው በጣት ከሚቆጠሩ ቆፍጣና እና ቀብራራ ወዛዝርት መሀል አንዷናቸው፡፡ ወዳጄ ማስተማሩን ቀጥላለች (በነገራችን ላይ እድሜዋ ገፋ ያለ ሲሆን ምንም እኩል ባይሆንም ወደ እማማ በላይነሽ እድሜ ሰፈር ከአስር እና አስራ አምስት አመታት ቀደም የሚል ነው)፡፡   መቼም ስለ ኤች.አይ.ቪ. ኤድስ እና ስለ ኮንደም ለማስተማር ከምንጠቀማቸው ነገሮች ውስጥ ሁለት ዋና...