Skip to main content

Posts

Showing posts from June, 2012

እንቀርባለን!

           እንቀርባለን! የእንግሊዝ ሊግ ብቻ አፍጥጠን እያየን እኛ እንደምንችል በጭራሽ ዘንግተን በሩጫ ላዪ ብቻ ሁሉን ነገር ጣልን፤ ምንድነው መመካት ብቻውን በሩጫ ዘራፍ! እንቀርባለን እኛም በዓለም ዋንጫ፤ ህዝባችን ዪዘፍናል በአንድነት ተቃቅፎ "ኢትዮፒያ መመኪያ"ን ከፍ አረጎ ለፍፎ፤ ማን ያውቃል ዪታያል ፖስተር ተለጥፎ ሰላሀዲን ሰኢድ ዋንጫ ሲስም ታቅፎ፡፡ መታሰቢያነቱ ለሳለህዲን ሰኢድ  አኒቲ

ቻዪና እንዳታገቡ!

መፍታቱን ፈታሽ ኝ ትዳሬን በተንሽው የወለድሽ ል ኝን ልጅ በባዶ ቤት ጣልሽው ብሎ ቢሳካልሽ የፈለግሽው ነገር ጡት አጥቶ በእሪታ እንዲያለቅስ ነበር ነበር የፈለግሽው ሲጨንቀኝ ለመስማት እንድለማመጥሽ በጡት ማጣት ምክንያት ቻዪና ነኝ እወቂ ሲፈቱኝ ፈታለሁ እራሴ እያጠባሁ አሳድገዋለሁ ጡትሽን እሚተካ ሌላ ጡት ሰራለሁ፡፡ መታሰብያነቱ ነጭ ለሚያድኑ የወገኔ አናዳጅ ችኮች ዪሁንልኝ፡፡                                                           አኒቲ

አላረጀሁም አላረጅም

እርጅና አፍጥጦ፣ በግላጭ ቢመጣ ፊትን አጨማዶ፣ መልኬ ቢገረጣ፤ እጄን አልሰጠውም፣ ወደላዪ አንስቼ እኖራለሁ ገና፣ መች ጠገብኩ በልቼ፤ በብእሬ ጫፎች፣ እያልኩኝ ብኩራራ በልበ ሙሉነት፣ ብጨፍር ባወራ፤ ሳላስብ ሳላውቀው፣ ሚስጥሩም ቢገባኝ የአርጅና ወንድም፣ ሞት መቶ ወሰደኝ፡፡ መታሰብያነቱ  ለጋሽ ስብሀት ይሁንልኝ፡፡                                         አኒቲ