Skip to main content

Posts

The Historic Chaltu Speeks Out

Let me paint you the picture of what happened in ATL yesterday. Me and Riyad S abona walking, minding our own business and we see an anti-Jawar protest happening 200 yards away from the meeting entrance. The police directed us to walk in closer to the side of the protest to avoid obstructing traffic.  So we saw their flags and I decided to take out my Oromo flag and walk.  First, it was just the slurs, calling me Galla. Then it was the spit, in front and behind me and then one made it with the perfect aim to hit my cheek. I continued to walk with my head high with the utmost respect until one 'balance' thought it would be okay to reach over and snatch my flag. He thought he got the flag, but I killed that dream, but as soon as he reached again and grabbed my hijab, I turned around and his face hit the back of my hand (like how words can change everything?). Lol, I actually slapped the hell out of him. When I looked back they were grabbing on Riyad's trad...
Recent posts

ከዶ/ር መረራ አስለቃሽ ጭስ አንዷ

ዶር መረራ ጉዲናን ሁላችንም እንደምናውቃቸው፣ በሀገራችን የመማር ማስተማር እና የፖለቲካ ምህዳር እንደ አስተማሪም እንደ አማራሪም በመሆን ከፍተኛ ሚና የተጫወቱና አንቱታን ያተረፉ የሀገራችን ዜጋ ናቸው።  አንደበተ ርቱ ባይባሉም መናገር የፈለጉትን ነገር ከመናገር ወደኋላ የማይሉ፣ ንግግራቸው ግልፅ እና ግልብ ከሚባል ተርታ ይመደባል ባይ ነኝ። እሳቸው ተናግረው አልያም ተከራክረው ፈገግ ያላልኩበት አጋጣሚ ትዝ አይለኝም። ከሰሞኑን የመታሰራቸውን ነገር በሰማሁ ወቅት፣ አንደ ወዳጄ አቀልድ ማህደሩ ይሁን አዚዓ ማህደር እነወጃ፣ አሉ ብሎ ካካፈለኝ ፈገግ የምታሰኝ ንግግራቸውን ላካፍላቹ ወደድኩ። ነገሩ የሆነው ፓርላማ ሳሉ ነው አሉ። የወቅቱ አፈጉባኤ ደግሞ ክቡር አቶ ተሸመ ቶጋ ነበሩ። አናም የመናገር እድሉ ሲደርሳቸው አቶ ተሾመ፣ ባላቸው ማይኩን የመዝጋትና የመክፈት ስልጣን፣ ቀጥል ብለዉት ደር መራራን እንዲናገሩ ፈቀዱላቸው። እናሎ ታድያ ወቅቱ የፓርላማው አመታዊ ሪፖርት በጠቅላይ ሚንስትሩ የሚቀርብበት ነበር፣ እንደሚታወቀው ዶር መረራ ቡዙን ግዜ ፓርላማ ላይ የማይቀሩበት አጋጣሚ ይህ እንደሆነ ይታወሳል። ይህንንም አጋጣሚ በመጠቀም (ቢቆራረጥም) ሚዲያውን በአግባቡ ይጠቀማሉ። ዶር መረራ ጀመሩ ፦ "ሲለ ተሰጠኝ እድል ባመሰጊን፣ ‘ፉት ሲሏት ጭልጥ’ እንደሚለው ተረት ቲሆናለች እና የተሰጠን ሰዐት ኢሀዴግ…" ብለው ሳይጨርሱ፣ አፈጉናኤው እላያቸው ላይ ማይኩን ጥርቅም አድርጉት። አፈ ጉባኤው:– "ደ/ር መረራ ሌላ ሌላውን ይተውና አጊባብነት የለው ጥያቄ ያቅርቡ፣ ጥያቄዎት ወይም አስታየቶ ክብር ሚኒስትሩ ባቀረቡት ሪፖርት ላይ ብቻ ይሁን፣ ከተሰጦት ሰዓት 5 ደቂቃ ብቻ ይቀሮታል" ቁጣን ባለው ለዛ ብለው  እንዳበቁ...

አምስት ለ አንድ?

በተጠናው ጥናት፤ ባረግነው ሙከራ እያለ ሲያቃዠን፣ የዛሬ ግዜ እውቀት፣ ሆኖብን መከራ፤ ሼም የለውም ሣይንስ፤ እንደው ጉድ አይፈራ እንስማው አንስማው? ከእግር ከፍ በሉ፣ ሲለን ለሠገራ፡፡ ለማረጋገጫ፣ Lab እንኳን ባይኖረን መቀበል አይከፋም፣ ሳይንስ ካለችሁን እንቀበላለን፡፡ ዳሩ ግን … ኮንዶሚንየሙ፤ የየቤቱ ጥበት ስለሚያስጨንቀን የእግር መስቀያ፣ ተጨማሪ ወጪ፣ እንቃወማለን፤ ለማጣጣል ሳይሆን፣ ሳይንስ ስለሆነ፤ ሳይንሱ ልክ ነው ለኛ ለሀገሬው፤ መፍቴሄውም ቀላል ነው ሲንኩን ዞር አድርጎ፣ ወደ ቀድሞ ጉርጓድ፤ ቶሎ መመለስ ነው፡፡ ግን ግን … ወጪን ብናስቀርም፣ ይህንን ተግብረን የማይካድው ሀቅ፣ ሀገራዊ ችግር፣ አንዲት ጉድፍ አለን አልሞ መተኮስ፣ አነጣትሮ ማራት፣ ለጉድ ነው ሚያቅተን፡፡ በተለይ በተለይ …  ካምፓስ ዩንቨርሲቲ፣ ሽንት ቤት ፍለጋ፣ ድንገት ጎራ ካልን  የኛ ሠው እንዲ ያራል? ብለን ባለማመን፣ እንደመማልን ቀበሌ ሲለጠፍ፣ ሲባል ከአር ነፃ፤ ደግመን እንጠይቅ፤ እና ምን ተሻለን? የተማረው ምሁር፣ አልሞ ካላራ ከቀበሌ እንዲማር፣ ምን ስራ ይሠራ??? ለዚህም አምስት ለ አንድ እንዳትሉኝ ብቻ፡፡ © Aniti to read more about this new development go to  http://www.lacocinaalternativa.com/2012/10/03/como-defecar-correctamente/

ስትሄጅ አትንገሪኝ

ምንም አትበይኝ፣ ስትሄጂ ጥለሺኝ ዝም ብለሽ ሂጂ፣ መሄድሽን ሳትነግሪኝ፤ ከኔጋር ለመሆን፣ ልብሽ ባይፈቅድልሽ መንገዱ ግን ይቅናሽ፣ ክፋም አይግጠምሽ፤ ፍቅርሽን መሸከም፣ ጫንቃዬ ባይችልም ከኔ ጋር ሁኚ፣ ብዬ አላስገዽሽም:: መሳቅ ሲያስፋልገኝ፣ በትዝታ አይሻለሁ ማልቀስ ቢያስፈልገኝ፣ ብቻዬን ቁጭብዬ እነፈርቃለሁ፤ በቃ በቃ ሂጂ፣ ዞር ብለሽ አትይኝ ሆዴን አታባቢው፣ ቻዎም አትበይኝ፤ ድምዕሽን አጥፊና፣ ኮቴሽን ጠብቀሽ ሳታንኮሻኩሺ፣ ውጪ ልቤን ዘግተሽ ቁልፉን ግን አስቀምጪው፣ አደራ ይሁንብሽ፡፡ ታዬ አለሙ 2005 ዓም ትንሽ ማስተካከያ ›› በአኒቲ

እናት - ያው - እናት - ናት!

በዚህ በኩል -  ህጉን ጣስሽ ብሎ፣ ያመናጭቃታል የደኑ ጥበቃ፣ ይተናኮላታል ፣   ሊያስር ያሳዳታል ሸክሟን ያስጥላታል፣ በባዶ ይሰዳታል ለእሷ ምግቧ ነው፣ ጉርሷ ይጨንቃታል፤ እውነት ለመናገር፣ አሷስ መቼ ጨንቋት ከእሷም ጉርስ በላይ፣ አለ ሚያሳስባት እንዲ አስጠግርሮ፣ ወገቧን ሚቆርጣት የሀረጓ ቅጣያ፣ የማህፀኗ ክፋይ ፣ የይሆናል እዠት መቼስ ገመተና? ይችል እንደሆነ፣ አንድ እንኳ ሊኖራት፤ ሲርበው የሚያለቅስ፣ ሲጠግብ የሚቧረቅ፣ ሄኔ ያስተኛችው ማንያውቃል ይኖራት ይሆናል፣ ባለማወቅ ብቻ፣ ብዙ የወለደቸው ተርቦ ሚገባ፣ ይማርልኝ ብላ፣ ትምህርት የላከቸው፡፡ ተሸክማ ደክማ፣ ጎብጣና ገርጥታ፣ ሆና ያልተሻለች ከዛሬ ህይወቷ፣ የተሸለ እንዲኖር፣ ለልጇ የተመኘች ፤ አመጣጡን ያውቃል፣ ጠንክሮ ይማራል ከግቡ ላይ ደርሶ፣ ላቤን ይጠርገዋል ፤ ምን ያደርጋል ታድያ፣ በሕልም ዓለም ስትስል ተጨናገፎ ቢቀር፣ የልቧን ሣያክል:: ዛሬን እንዳረጀች፣ የጇን መች አገኘች ህልሟ መች ተሳካ፣ መች ምኞቷን ኖረች ከአሁን ቡሀላ፣ መችስ ትኖራለች፤ ተስፋዬ ያለችው ገና ነፍሱን ሳያውቅ፣ ሱስ ቀድሞ እያወቀ ጠንክሮ እንደመስራት፣ በወሬ እየሞቀ፤ ላይብረሪ እያለ፣ ፑል-ቤት ሄዶ መዋል አዳር ላጥና ብሎ፣ በጭፈራው መጋል ከማይሆኑ ገጥሞ፣ እነሱን ለመምሠል፤ ልፋቷን በትኖት፣ ዋልጌ ሆኖ ቀረ፣ ገና በ ሀይ-እስኩል፡፡ ከወገቧ ጉብጠት፣ ከሸክሟም ክብደት ልቧ እንዳይሠበር፣ ሁሉም ፍቅር ይስጣት የኛ እናት ባትሆንም፣ በሠፈር ካወቅን፣ እንደዚህ ያለች ሴት ብቻዋን እንዳቱል፣ ሄደን እናጫውታት፣ ካለንም እንርዳት በዓልም ሲደርስ፣ እንሂድ እናፅናናት፣ እንደ ልጅ እንሁናት ቸ...

እየኖሩ ሞት

ሠምተን ስትሠቃይ፣ ከነጎድን ትተናት እየቻልን ማቅናት፣ ከጎን ቆመንላት በግዴለሽነት፣ ረጋግጠን ካለፍናት ትርጉሟ በተግባር፣ መስጠት ከሌለባት መኖር ምን መኖር ናት? ለራስ እየበሉ፣ ሌላ ተርቦባት ለራስ ተጋጊጠው፣ ይሄ ታርዞባት ቤቤት ተጠልለው፣ ተርፎ እያከራ ዩ ት፤ በራስ መውደድ ጠኔ፣ በየቁም ድንዝዛት ሲያድር ሠው ትቦ ውስጥ፣ አይተው እንዳላዩት ሢያስል በክረምቱ፣ ሠምተው እንዳልሠማት:: እንኳን እና ገንዘብ፣ ወይን የቁስ ንብረት መች የማያስከፍል፣ የልብ ፍቅር ሠጡት ቆሻሻ እያረጉት፣ ነጣቂ  ነው አሉት ምክንያቱን ሳያያዩት፣ ቀርበው ሳይረዱት የአደም ልጅ መሆኑን፣ እያወቁ ሳቱት፡፡ መኖር ሳትሆን ይቺህ፣ የማይሠጥ ሠው ህይወት ያለምንም ለቅሶ፣ ያለአንዳች ግንዛት እየተነፈሱ እየተራመዱ፣ እያካበቱባት ሀፍት እየታዩ እያሉ፣ እየኖሩ ሞት ናት፡፡ ሐምኔ 15፣ 2005 © አኒቲ 

በብሄራዊ ቡድኑ መቀጣት የተነሣ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ ባጃጆች የሥራ ማቆም አድማ ሊያደርጉ ነው፡፡

ኢትዮጵያ ከደቡብ አፍሪቃ ባስመዘገበችው የዓለም ዋንጫ ማጣርያ ማሸነፍ ምክንያት ህዝቡ ሲያደርገው በነበርው ሀገር አቀፍ የፈንጠዝያ ዱብእዳ በተለያዩ የሀገሪቷ ትልልቅ ከተሞች (ማለትም መቀሌ፤ ባሕር ዳር፤ አዳማ፤ ሐዋሳ እና ሌሎችም) ውስጥ የሚኖሮ፣ ህንድ ሠራሽ ኢትዮጵያ ነዳሽ ባጃጆች ላያ ይህ ነው የማይባል የሰብዓዊ መብት ረገጣ በማከናወናቸው ምክንያት፣ በዛሬው እለት ባጃጆቹ ተወካዮቻቸውን መርጠው አዲስ አበባ ወደሚገኘው የህንድ ኢንባሲ መላካቸው ተገለፀ፡፡ የውስጥ ምንጮች ለዜና አውታራችን እንዳስረዱት ከሆነ፣ ጉዳዩን እስከዛሬ ችላ ብለው የቆዩት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን እውነትም ለማጣሪያው አንድ ቀሪ ጫወታ እያለው በቀጥታ ማለፉን በመስማታችን እና በመስማማታችን ነው፣ ሲሉ ነገር ግን ለዛሬው አቤቱታ ያበቃቸውን ነገር ከመቀሌ የተመረጡት ህንድ ሠራሽ ሀበሻ ነዳሽ ታርጋ ቁጥራቸው  ኮድ 1   መ ቀ- 2334  የሆነው ባጃጅ እንዳሉት፤ “ሁለት ምክንያት  ለዚህ አቤቱታ እዚህ አዲስ አበባ ወደሚገኘው ሀገራችን የህንድ ኢንባሲ አምጥቶናል:: አንደኛው ነገር እኛ ለዚህች ሀገር እንሥራ እንጂ ዜጋዋ አይደለንም፣ ዜጋዋ ብንሆን ኖሮ እንዲህ ያለ ከፍተኛ ጉዳት እና ከፍተኛ የሞራል ውድቀት በራሳችን ወገን አይደርስብንም ነበር፤ ሆኖም ግን በሠው ሀገር እንደመሆናችን እና በተገኘው ውጤት የምናገለግለው ህዝብ ምንም ቢረግጠንም ተደስቶ ማየታችን ጥሩ ሆኖ ሳለ እስከዛሬም ዝም ብለን ችለን ዛሬ ግን ነጥብ መቀነሱን በመስማታችን እኛም እንዲህ ላለ ከንቱ ጉስቁልና መዳረጋችን ስላሳዘነን ነው አቤት ለማለት የመጣነው”  በማለት የተሠማቸውን ሀዘን ድብልቅልቅ ባለ ስሜት ገልፀውልናል፡፡ በሌላ በኩል ከሐዋሳ ተወክለው የመጡትን ታ...