Skip to main content

Posts

Showing posts from November, 2012

ለዳግመኛ ፍቅር!

የባጡን የቆጡን ማህላ እየማልኩልሽ ልሰቀል ነው ልሞት ብዬ ጎተጎትኩሽ ልብሽን ሸርሽሬ የእኔ የብቻዬ ትሆኝ ዘንድ አረግኩሽ፤ የት ይደርሳል ሲባል አይን ውስጥ ገባሁና እንደ በሬው ሆንኩኝ ቄራ ታየሁና፡፡ አንቺ እያለምሽኝ ያገባኛል ብለሽ ሳላገባሽ ቀረሁ መጥፎሽን አግዝፌ ቀስ ብዬ ሸሸሁ ጥሩሽን ሸሽጌ ገላ ጠረንሽን አሽቼ ብጠግበው፤ እውነት ለመናገር ዛሬ ላይ ቁጭብዬ ትላንትን ስለካ ‘በእጅ-ያለ-ወርቅ …..’ እንዳሉት፣ ውስጤ ይፀፅታል በሚዘው አይረካ፡፡ እስካሁን ብቆይም፣ ደብቄሽ ስሜቴን፣ አልሸነፍ ብዬ ሲያይሽ ልቤ እንደ አዲስ፣ ወጥተሽ ከጉያዬ፤ እንዳልሆነ ምንም፣ አንቺን ሲመለከት የሚያደርገው ነገር፣ እንደሆነ ውሸት፤ በእናቴ ምላለው፣ እየታገለው እንጂ፣ የልቡን መፀፀት ፊቴ-ይናፍቀዋል፣ ፊቴ ያስፈልገዋል፣ የያኔው ፈገግታ የያን ግዜው ስሜት፡፡ እውነት የኔ ፍቅር፣ እውነት ለመናገር ያዛኔን ሽርሽር የየያኔ ገላሽን፣ ለሊት እንኳ ሳይቀር፤ ቀንማ ምንላድርግ፣ አምረሽ እያየሁሽ ፈርቼ ተዋለሁ ለሊት ማን ከልክሎኝ፣ እኮመኩማለሁ የያኔው አልበሜን፣ ላይሽ ከፎቶዬ፣ እንደከሰረ ዓረብ አገላብጣለሁ፡፡ ዓይኔን በጨው ባጥብም፣ ባይሠማኝ ዩሉኝታ እድል ስጪኝ ውዴ፣ እስኪ ለአንድ ላፍታ፤ ልቤ ልብ ገዝቶ፣ ለመመራት መቷል፣ የይቅርታን ቦታ አጢኚው ደጋግመሽ፣ ይህን አቤቱታ፡፡ ገንፍሎ ሲያገረሽ ፣ ሆንሽና ስራዬ መጣሁ ያንቺ ጠላት፣ ሁለቴ ልማረክ፣ እጅ ወደላይ ብዬ ነጠላ አዘቅዝቄ፣ ቅንድቤን ላጭቼ፣ እያለቃቀስኩኝ ውስጥሽን ገድዬ፤ ከደሙ እንደነፃ፣ ለቅሶው ላይ ያቆመኝ ምክንያቱን እወቂ፣ በዳግመ-መውደድሽ፣ በ ዳግመኛው-ፍቅርሽ ፣  አቅሌን ስላጣሁኝ፤ እንደ እጣ ወጥ...

የማግብያ ፈተና (ለትዳር)

የድሮው ተማሪ የያኔ ጠብሼ ኦልድ ካሪኩለም በፍቅሬ አንግሼ፤ ለስሙ ተምራ ምሁር ተብላለች በዚያ የዋህ ዘመን ሥራ የተቀጠረች፤ እናላእሁ ታድያ አሁን በቀደም ለት ሥራ ቀይር ብላ ማንበብ ቢያስፈልጋት፤ በአንድ ቢሮ ፊርማ ጫማዋን ማንጠልጠል መስቀል ቢደብራት መዋሉን ጀመረች ቀኑን ሙሉ ስትዞር እንጀራ ሲያዞራት፤ ለሷ የሚመቻት የምታውቀው ቢኖር የአዲስ ዘመን እትም አልያም ሪፖርተር፤ ethio-jobs ብል አታርፈው ነገር ተሰታ ትውላለች ከአራትኪሎ ደጃፍ እስከ ታች ለገሀር ለብይ ጫወታ ሲንፏቀቅ እንደዋለ ጨቅላ ህፃን በሠፈር እማስታወቂያ ደጅ ከጋዜጦች መንደር፤ ሼም ደግሞ የላትም ሁሌም ትዝታለች ትምህርት ድሮ ቀረ በኛ ግዜ እያለች፡፡ እውነት ለመናገር የትምህርቱ ጥራት የያኔ ይሻል ነበር፤ ቅሉ ምን ያደርጋል ታበሳጨኛለች IT አታርፍም ታሳዝነኛለች፤ Technology ነገር ያጥወለውላታል Computer ስታይ ነስር ይነስራታል፤ እንኳን እና facebook አንድ email የሌላት ግራ ነው ሚገባኝ ዘወትር ሳስባት፤ እንደ እኔ እንዳትሆኑ ህይወቴን ያያቹ እናም ጨምሩበት በያዛቹት መስፈርት እንደዚህ ብላቹ፤ ለም ት ጠብሱት ጥብስ ለነጌ አጋራቹ ለሚስት ብቻ ሳይሆን ብሎም ለባላቹ የማግብያ ፈተና Computer Literate መስፈሪያ ይሁናቹ እጅጉን እንዲያምር እንዲዘልቅ ፍቅራቹ፡፡ Aniti Nov, 2012 For the girl lol