Skip to main content

የፈጠራ ሥራ ውድድር ማስታወቅያ

የኢትዮጵያ የኬሚስት ባለሞያዎች ማህበር በሀገሪቷ እድገት ውስጥ ያለውን ሚና ከፍ ለማድረግ፤ እነደ መቋቋሙ መጠን አስካሁን ተጨባጫ የሆነ ተግባርን ሳያከናውን ቆይቷል፡፡ 

ሆኖም ግን ሀገራችን እያስመዘገበች ያለው እድገት፣ ተነሳሽነታችንን በእጅጉ እንደሚያነቃቃ በማመን፣ ማህበሩ ለውድድርነት ይሁን ዘንድ ይህንን የመወዳደሪያ ዘርፍ ለመጀመርያ ግዜ ማስለፈፍ አስፈልጓል፡፡

ተፈላጊ ችሎታ፡-

በኬሚስትሪ ወይም በኬሚካል ኢንጂነሪንግ ከታወቀም ወይም ካልታወቀም ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ወይም የመጨረሻ  ዲግሪ ያለው ወይም ያላት፡፡

የመወዳደሪያ ዘርፍ፡-

ሀገር በቀል አረቄ፡፡

የውድድሩ አስፈላጊነት፣ ግብ እና አላማ፡-

የሚከተሉት አምስት ነጥቦች ለውድድሩ አስፈላጊነት እንዲሁም የትግበራው የረጅም እና የአጭር ግዜ ግብ እና አላማዎች ናቸው፣

1.      ሀገራችን ያሉ ኬሚስቶችን በፈጠራ ሥራ ላይ ማበረታታት፡፡
2.     የሀገራችን ኬሚስቶች፣ በሀገር እድገት ውስጥ፣ (ከማስተማር እና ከመማር ባሻግር) ሊኖራቸው የሚገባውን ተጨባጭ ሚና፣ ማጠናከር፡፡
3.     በፎርሙላ ማጣት ሳቢያ፣ አረቄ አውጪ ባልቴቶች፣ ለረዠም ግዜ ለኪሳራ እና ለስነልቦና ችግር እንደመጋለጣቸው መጠን፣  እስታንዳርዱን የጠበቀ የአረቄ ፎርሙላ በማውጣት በሀገር እኮኖሚ ላይ እየደረሰ ያለውን ውድመት መታደግ፡፡
4.     ለኢትዮጵያ አረቄ አውጪዎች እና ቸርቻሪዎች ማህበር፣ ሳይንሳዊ ድጎማ በመስጠት አትራፊነታቸውን ማጠናከር እና በሀገር እድገት ውስጥ ያላቸውን ሚና ማሳደግ፡፡
5.     በመጨረሻም፣ እንደ ቡና ላኪዎች ማህበር፣ የአረቄ ላኪዎችን ማህበር በማቋቋም እና ብርዳማ በሚባሉ፣ እንደ ራሺያ፤ ዩክሬን፤ ምእራብ ቻይና፤ በከፊል ካናዳ እና አውስትራሊያ ውጤቶችን የሚያስተዋውቅ ተጓዥ የንግድ ተርዒት በማዘጋጀት ገበያን ማፈላለግ፣ ዋና ዋና ግቦቹ ናቸው፡፡

የሽልማት አይነት፡

1ኛ  ለወጣ  -  በሥዕሉ ላይ የሚታየውን ሙሉ የአረቄ ማውጫ ሀገር በቀል ማሽን የሚሸለም ሲሁን፡፡
2ኛ ለወጣ  -   በአረቄ ማውጣት እና መቸብቸብ የምትታወቀዋን አርሲ ነጌሌ ከተማን ጓዲያ ጎድጓዳ ለመጎብኘት የሚያስችል 
               የአንድ ሳምንት የጉብኝት ወጪ እና ደርሶ መልስ የሎንቺና ትኬት፡ (በነገራችን ላይ በዛው መኮብለል የተከለከለ  ነው)፡፡
3ኛ ለወጣ   - አንድ ጀሪካን አረቄ፡፡


ማሳሰቢያ፡

ደረጃዎቹን የሚለዩ ታዋቂ የኪሚስትሪ ምሁራን ነን ባይ ዬኒቨርሲቲ መምህራን ብቻ ሳይሆኑ፣ የአንበሳውን ድርሻ የሚወስዱት በአርሲ ነጌሌ የሚገኙ አንቱታን ያተረፉ ቀማሾች ይሆናል፡፡


የውድድሩን መስፈርቶች የሚያሟላ እና የተጠቀሱትን ግብዓቶች (ፎርሙላዎችን እና እስትራቴጂዎችን) በመቅረፅ፣ እስከ ፊታችን እሁድ ከሠዓት ቡሃላ ድረስ፣ ፌስ-ቡክ  www.facebook.com/anitifunnypic ላይ የሚገኘውን የ Like ቁልፍ በመጫን፣ ምንም አይነት የባንክ ሲፒኦ ሳያሲዝ፣ ማንኛውም ተወዳዳሪ መወዳደር የሚችል መሆኑን ደስታና ሀዘን በተቀላቀለበት ስሜት እንገልፃለን፡፡

ከሠላምታ ጋር


እትዬ ብርቄም አረቄ
በኢትዮጵያ ኬሚስቶች ህብረት፣ የአረቄ ዘርፈ ማስፋፊያ ስራ ሂደት ባለቤት፡፡


‹መማር መማር፤ አሁንም መማር›› ሳይሆን

‹‹መማር መማር መማር፣ በተማሩት ነገር፣ ያከባቢን ችግር ለመቅረፍ መሞከር››

Comments

Popular posts from this blog

The Historic Chaltu Speeks Out

Let me paint you the picture of what happened in ATL yesterday. Me and Riyad S abona walking, minding our own business and we see an anti-Jawar protest happening 200 yards away from the meeting entrance. The police directed us to walk in closer to the side of the protest to avoid obstructing traffic.  So we saw their flags and I decided to take out my Oromo flag and walk.  First, it was just the slurs, calling me Galla. Then it was the spit, in front and behind me and then one made it with the perfect aim to hit my cheek. I continued to walk with my head high with the utmost respect until one 'balance' thought it would be okay to reach over and snatch my flag. He thought he got the flag, but I killed that dream, but as soon as he reached again and grabbed my hijab, I turned around and his face hit the back of my hand (like how words can change everything?). Lol, I actually slapped the hell out of him. When I looked back they were grabbing on Riyad's trad...

ከዶ/ር መረራ አስለቃሽ ጭስ አንዷ

ዶር መረራ ጉዲናን ሁላችንም እንደምናውቃቸው፣ በሀገራችን የመማር ማስተማር እና የፖለቲካ ምህዳር እንደ አስተማሪም እንደ አማራሪም በመሆን ከፍተኛ ሚና የተጫወቱና አንቱታን ያተረፉ የሀገራችን ዜጋ ናቸው።  አንደበተ ርቱ ባይባሉም መናገር የፈለጉትን ነገር ከመናገር ወደኋላ የማይሉ፣ ንግግራቸው ግልፅ እና ግልብ ከሚባል ተርታ ይመደባል ባይ ነኝ። እሳቸው ተናግረው አልያም ተከራክረው ፈገግ ያላልኩበት አጋጣሚ ትዝ አይለኝም። ከሰሞኑን የመታሰራቸውን ነገር በሰማሁ ወቅት፣ አንደ ወዳጄ አቀልድ ማህደሩ ይሁን አዚዓ ማህደር እነወጃ፣ አሉ ብሎ ካካፈለኝ ፈገግ የምታሰኝ ንግግራቸውን ላካፍላቹ ወደድኩ። ነገሩ የሆነው ፓርላማ ሳሉ ነው አሉ። የወቅቱ አፈጉባኤ ደግሞ ክቡር አቶ ተሸመ ቶጋ ነበሩ። አናም የመናገር እድሉ ሲደርሳቸው አቶ ተሾመ፣ ባላቸው ማይኩን የመዝጋትና የመክፈት ስልጣን፣ ቀጥል ብለዉት ደር መራራን እንዲናገሩ ፈቀዱላቸው። እናሎ ታድያ ወቅቱ የፓርላማው አመታዊ ሪፖርት በጠቅላይ ሚንስትሩ የሚቀርብበት ነበር፣ እንደሚታወቀው ዶር መረራ ቡዙን ግዜ ፓርላማ ላይ የማይቀሩበት አጋጣሚ ይህ እንደሆነ ይታወሳል። ይህንንም አጋጣሚ በመጠቀም (ቢቆራረጥም) ሚዲያውን በአግባቡ ይጠቀማሉ። ዶር መረራ ጀመሩ ፦ "ሲለ ተሰጠኝ እድል ባመሰጊን፣ ‘ፉት ሲሏት ጭልጥ’ እንደሚለው ተረት ቲሆናለች እና የተሰጠን ሰዐት ኢሀዴግ…" ብለው ሳይጨርሱ፣ አፈጉናኤው እላያቸው ላይ ማይኩን ጥርቅም አድርጉት። አፈ ጉባኤው:– "ደ/ር መረራ ሌላ ሌላውን ይተውና አጊባብነት የለው ጥያቄ ያቅርቡ፣ ጥያቄዎት ወይም አስታየቶ ክብር ሚኒስትሩ ባቀረቡት ሪፖርት ላይ ብቻ ይሁን፣ ከተሰጦት ሰዓት 5 ደቂቃ ብቻ ይቀሮታል" ቁጣን ባለው ለዛ ብለው  እንዳበቁ...

የድንቅነሽ/ሉሲ በደህና የመመለሷ ነገር . . .

ዛሬ ድንገት ኢቲቪ ተከፍቶ ዜና ሠማሁኝ እና ከዜናው አንዱ ትኩረቴን ሳብ አድርጎት ጆሮዬን ቀልቤን አቅሌን ሙሉ ለሙሉ ለኢቲቪ ሰጠሁ፡፡ ታድያሎ ያልኳችሁ ዜና እናንተም የሰማችሁት ያ ስለ ድንቅነሽ /ሉሲ/ ከ5 ዓመት ቆይታ ቡሀላ ከወደ አሜሪካን ሀገር ተመለሰች የሚለው ነበር፡፡ ገና የዜናው ርዕስ እንደሰማሁኝ ነበር፤ እንኳን በደህና ሄደሽ ባልልም፤ እንኳን ደህና መጣሽ ማለቴ ግድ ነበር፤   እናም አልኩኝ፡፡ ሙሉ የዜናውን ሀተታ እና የምስል ቅንብር ስመለከት፤ለርክክቡም አሜሪካዊ እና ታዋቂ ብሎም አዋቂ የኢትዮጰያዊ ተመራማሪዎች ከአሜሪካን ድረስ እዚህ መገኘታቸውን ሠማሁ፡፡ ከዛማ እንኳን በደህና ተመለስሽ ያልኩት አባባል ግልፅነት እና ተጠያቂነት የጎደለው ደብዛዛ ምስክርነት መስሎ ታየኝ፤ ጥርጣሬም ወረረኝ፡፡ ለምን እና እንዴት ካላችሁ. . . . . የ እኛ ምሁራን ሉሲን ገቢ ያደረጉበት የማረጋገጫ መለኪያ ተጠቀምን ያሉት ስልት እንደ ስለት አሳቀቀኝ፡፡ ፕሮፌሰሩ ቃል ሲሰጡ፤ “እያንዳንዷን አጥንት መዝነን፣ ለክተን ነው የተቀበልነው::” በዜናው ላይ የቀረበው የ ርክክብ ቪዲዮ ላይ እንዳየነው፤  እና መገለጫችን የሆነውን የሉሲን አፅም ለዛውም ለ5 ዓመት ያህል ሠው ቤት ቆይቶ እንደሚመለስ ብርቅዬ ቁስ ሳይሆን እንደ አሞሌ ሲቀባበሉ መመልከቴ አስገርሞኛል፡፡ በተለይ በተለይ የእኛው ምሁራን ይህችን በስንት ምርምር የእድሜ ጠገብነቷን ሚስጢር በዓለም አቀፍ ደረጃ ለመለየት ብዙ ምርምር የተደረገላትን በክብደት እና ቁመት በመለካት ማረጋገጥ ችለናል ማለታቸው አግራሞት ፈጥሮብኛል፡፡ እኔ የምለው እንደው ደረጃ መዳቢዎች ባለስልጣን እራሱ ዘይትን ከውጪ ለማስገባት ምን ያህል የላብራቶሪ ፍተሸ እናደሚያካሂድ ባለፈው ዘይት እንትን ያ...