የኢትዮጵያ የኬሚስት ባለሞያዎች ማህበር
በሀገሪቷ እድገት ውስጥ ያለውን ሚና ከፍ ለማድረግ፤ እነደ መቋቋሙ መጠን አስካሁን ተጨባጫ የሆነ ተግባርን ሳያከናውን ቆይቷል፡፡
ሆኖም ግን ሀገራችን እያስመዘገበች ያለው እድገት፣ ተነሳሽነታችንን በእጅጉ እንደሚያነቃቃ በማመን፣ ማህበሩ ለውድድርነት ይሁን
ዘንድ ይህንን የመወዳደሪያ ዘርፍ ለመጀመርያ ግዜ ማስለፈፍ አስፈልጓል፡፡
ተፈላጊ ችሎታ፡-
በኬሚስትሪ ወይም በኬሚካል ኢንጂነሪንግ ከታወቀም
ወይም ካልታወቀም ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ወይም የመጨረሻ ዲግሪ
ያለው ወይም ያላት፡፡
የመወዳደሪያ ዘርፍ፡-
ሀገር በቀል አረቄ፡፡
የውድድሩ አስፈላጊነት፣ ግብ እና አላማ፡-
የሚከተሉት አምስት ነጥቦች ለውድድሩ አስፈላጊነት
እንዲሁም የትግበራው የረጅም እና የአጭር ግዜ ግብ እና አላማዎች ናቸው፣
1.
በሀገራችን ያሉ ኬሚስቶችን በፈጠራ ሥራ ላይ ማበረታታት፡፡
2.
የሀገራችን ኬሚስቶች፣ በሀገር
እድገት ውስጥ፣ (ከማስተማር እና ከመማር ባሻግር) ሊኖራቸው የሚገባውን ተጨባጭ ሚና፣ ማጠናከር፡፡
3.
በፎርሙላ ማጣት ሳቢያ፣ አረቄ
አውጪ ባልቴቶች፣ ለረዠም ግዜ ለኪሳራ እና ለስነልቦና ችግር እንደመጋለጣቸው መጠን፣ እስታንዳርዱን የጠበቀ የአረቄ ፎርሙላ
በማውጣት በሀገር እኮኖሚ ላይ እየደረሰ ያለውን ውድመት መታደግ፡፡
4.
ለኢትዮጵያ አረቄ አውጪዎች
እና ቸርቻሪዎች ማህበር፣ ሳይንሳዊ ድጎማ በመስጠት አትራፊነታቸውን ማጠናከር እና በሀገር እድገት ውስጥ ያላቸውን ሚና ማሳደግ፡፡
5.
በመጨረሻም፣ እንደ ቡና
ላኪዎች ማህበር፣ የአረቄ ላኪዎችን ማህበር በማቋቋም እና ብርዳማ በሚባሉ፣ እንደ ራሺያ፤ ዩክሬን፤ ምእራብ ቻይና፤ በከፊል
ካናዳ እና አውስትራሊያ ውጤቶችን የሚያስተዋውቅ ተጓዥ የንግድ ተርዒት በማዘጋጀት ገበያን ማፈላለግ፣ ዋና ዋና ግቦቹ ናቸው፡፡
የሽልማት አይነት፡
1ኛ ለወጣ - በሥዕሉ ላይ የሚታየውን ሙሉ የአረቄ ማውጫ ሀገር በቀል ማሽን የሚሸለም
ሲሁን፡፡
2ኛ ለወጣ - በአረቄ ማውጣት እና መቸብቸብ የምትታወቀዋን አርሲ ነጌሌ ከተማን ጓዲያ
ጎድጓዳ ለመጎብኘት የሚያስችል
የአንድ ሳምንት የጉብኝት ወጪ እና ደርሶ መልስ የሎንቺና ትኬት፡ (በነገራችን ላይ በዛው
መኮብለል የተከለከለ ነው)፡፡
3ኛ ለወጣ - አንድ ጀሪካን አረቄ፡፡
ማሳሰቢያ፡
ደረጃዎቹን የሚለዩ ታዋቂ
የኪሚስትሪ ምሁራን ነን ባይ ዬኒቨርሲቲ መምህራን ብቻ ሳይሆኑ፣ የአንበሳውን ድርሻ የሚወስዱት በአርሲ ነጌሌ የሚገኙ አንቱታን
ያተረፉ ቀማሾች ይሆናል፡፡
የውድድሩን መስፈርቶች የሚያሟላ እና
የተጠቀሱትን ግብዓቶች (ፎርሙላዎችን እና እስትራቴጂዎችን) በመቅረፅ፣ እስከ ፊታችን እሁድ ከሠዓት ቡሃላ ድረስ፣ ፌስ-ቡክ www.facebook.com/anitifunnypic
ላይ የሚገኘውን የ Like ቁልፍ በመጫን፣ ምንም አይነት የባንክ ሲፒኦ ሳያሲዝ፣ ማንኛውም ተወዳዳሪ መወዳደር የሚችል መሆኑን
ደስታና ሀዘን በተቀላቀለበት ስሜት እንገልፃለን፡፡
ከሠላምታ ጋር
እትዬ ብርቄም አረቄ
በኢትዮጵያ ኬሚስቶች ህብረት፣ የአረቄ ዘርፈ ማስፋፊያ ስራ ሂደት ባለቤት፡፡
‹‹መማር መማር፤ አሁንም መማር›› ሳይሆን
‹‹መማር መማር መማር፣ በተማሩት ነገር፣
ያከባቢን ችግር፣ ለመቅረፍ መሞከር››

Comments
Post a Comment