Skip to main content

በህዳሴው ግድብ ስም አስገራሚ ማጭበርበር


ሰሞኑን የወዳጄ ወዳጅ ከምሽቱ ሦስት ሠዓት ተኩል አከባቢ አንድ የስልክ ጥሪ ያስተናግዳል፡፡ 

ከበስተማዶ ያለው ደዋይ ድምፅ ሆነ ንግግር ቅልጥ ካለ የአየር ላይ የሬዲዮን ውይይት ይመስላል፡፡ መሆኑም አልቀረ በጣም ብዙ ልምድ ያለው ጋዜጠኛ የሚመስለው ግለሰብ ጎርነን ባለ ድምፅ 

‹‹ከኤፍ ኤም ነው ጤና ይስጥልኝ›› ብሎ ሠላምታውን ያቀርብለታል፡፡ የወዳጄ ወዳጅ ከማያውቀው የስልክ ጥሪ ባገኘው ሞቅ ያለ ሠላምታ ድንግርግር እያለ ፈጣሪን በማመስገን ምላሹን በሠላምታ ሠጠው፡፡

ከስልኩ ወድያ ማዶ ያለው ጋዜጠኛው ደዋይ ቀጥሏል  

‹‹…….. ይህ አዲስ የሬድዮ ፕሮግራም ዜጎች ለህዳሴው ግድብ ግንባታ ያላቸውን ርብርብ በዘለቄታው ለማነሳሳት እና በግድቡ ዙርያ ያላቸውን እውቀት ለማጠናከር በማሰብ የተዘጋጀ ነው፡፡ ፕሮግራሙ በታዋቂው የሀገራችን ባለሀብት አቶ (እከሌ) ድርጅቶች አማካኝነት እስፖንሰር የተደረገ ሲሆን የተለያዩ የሀገራችን ዜጎች ስልክ ላይ በመደወል ስለ ህዳሴው ግድብ አስመልክቶ 3(ሶስት) ጥያቄዎችን የምንጠይቅ ሲሆን ለሶስቱም ጥያቄዎች ሙሉ ምላሽ ለመለሱ የ 5000 (አምስት ሺህ) ብር ሽልማት አቅራቢያው በሚገኝ ባንክ አማካኝነት በመላሹ ስም ወይም በአካውንት ቁጥሩ እናስተላልፋለን፡፡›› 

በማለት ጠቅላላ አላማውን እና ሂደቶቹን በአጭሩ አስቀመጠለት፡፡

እናላችሁ የወዳጄ ወዳጅ የሠማውን ማመን እያቃተው፣ አረንጓዴው የመቶ መቶ የብር ረብጣ በፊቱ ውልብ እያለ፣ እድለኛነቱን በውስጡ እያደነቀ፣ መጓጓቱን በሚያሳብቅ ድምፅ 

‹‹ … እሺ አመሰግናለሁ ጠይቁኝ … (መግደርደሩን ለመግለፅ እና መጓጓቱን ላለማሳወቅ) እሞክራለሁ›› በማለት ለኤፍ.ኤም. ጋዜጠኛ ነኝ ባዩ ደዋይ የንግግሩን ቀጣይነት የሚያበስር ምላሽን ሠጠው፡፡

በነገሩ የተደሰተ በሚመስል ጥርት ያለ ድምፅ ‹‹በጣም ጥሩ በመጀመርያ ሙሉ ስሞትን እና ከየት የሀገራችን ክልል እና ከተማ እንደሆኑ ይንገሩን›› በማለት የመጀመርያውን ግን የማያስሸልመውን ጥያቄ በማስቀደም ወደሚያስሸልሙት ጥያቄዎች ተሸጋገረ፡፡

ጋዜጠኛው ቀጥሏል 

‹‹የመጀመርያው ጥያቄ ይሰማል አድማጫችን (እከሌ) አጠገብህ ሬድዮን ካለ ሙሉ ለሙሉ ዝጋው››፡፡

የወዳጄ ወዳጅ በቶሎ ቀበል አድርጎ ‹‹ኣረ ምንም ሬድዮን አጠገቤ የለም ዝግ ነው›› በማለት መለሰለት፡፡

‹‹ መልካም፣ የመጀመርያው ጥያቄ፣ የህዳሴው ድልድይ የሚገኝበትን ትክክለኛውን የሀገራችንን ክልል ጥቀስ………መለሠለት ……….. ትክክለኛውን መልስ መልሠዋል…….. ቀጣዩ ጥያቄ……››፡፡ እያለ እያለ ጋዜጠኛው ሶስቱንም ጥያቄ ሲጠይቅ፣ ተጠያቂውም መልሱን አንድ በአንድ በትክክል በመመለስ የ 5000 ብር ተሸላሚነቱን አረጋገጠ፡፡

መቋጫው ላይ፣ ‹‹የአብሮነት ቆይታችን ከማብቃቱ በፊት፣ ቀደም ሲል በመግቢያችን ላይ የጠቀስንልህን የገንዘብ መጠን አሸናፊ በመሆንህ፣ ሽልማቱን ትራንስፈር ይደረግልህ ዘንድ  በአቅራቢያክ የሚገኝን የባንክ ስም አልያም የባንክ አካውንትህን ትነግረናለህ›› ፡፡

ማመን እያቃተው፣ የባንክ የአካውቱ ረዘም ያለ ስለሆነ በቃሉ ስለማያስታውስ ብቻ ፈጠን ብሎ በሚኖርበት ከተማ የሚገኝን አንድ የባንክ ስም በመጥቀስ ሠጠው፡፡ ከስልኩ በስተጀርባ ያለው ጋዜጠኛ የሰማውን ባንክ ስም እና ሙሉ ስሙን ደግሞ ሲጠራ ‹‹ አዎን ››  የሚለውን የማረጋገጫ መልስም ከወዲህ ቢያገኝም የቀረ ሀሳብ እንዳለው ያስታውቃል፡፡

የወዳጄ ወዳጅ በዚያው ቅፅበት በውስጡ ‹‹… ደግሞ ምን ቀረ…..›› እያለ ቀጣዩን ሀሳብ ማዳመጥ ጀመረ፡፡

‹‹….. እንግዲህ አድማጫችን የዝግጅታችን ተካፋይ ሆነው ለተጠየቁት ጥያቄ ሙሉ መልስ በመመለሶ ተሸላሚ ስለሆኑ  በሬድዮን ጣቢያችን እና በእስፖንሰራችን ስም በድጋሜ እንኳን ደስ ያሎ ለማለት እንወዳለን፡፡››

‹‹…ለህዳሴውን ድልድይ ግንባታ ቀጣይነት ያለው ርብርብን በማስቀጠል ረገድ እርሶም እንደ አንድ ዜጋ ያለቦትን የዜግነት ድርሻዎን ይወጡ ዘንድ በኤሌከትሮኒክ ስልክ በአዲስ መልኩ እየተሸጠ ያለውን የ500 (አምስት መቶ ብር) የቦንድ ግዢ 5 (አምስት) ባለ መቶ ብር ካርዶችን ፍቀው በመላክ ለዚህ ታሪካዊ የተቀደሰ አላማ አካል ይሁኑ ዘንድ መልካም ፍቃዶን እንጠይቃለን፡፡›. ለነበረን መልካም ቆይታ እናመሰግናለን ደህና ይሰንብቱ፡፡›› ይለውና በመሰናበት ስልኩ ከወድያ ይዘጋል፡፡ 

ስልኩን ከዘጋው ቡሀላ ሀሳቡ በሁለት ቦታ ተከፈለ እደለኛነት አልያ እድለቢስነት፡፡ በንጋታው ወደ ጋራ ወዳጃችን ስልኩን ያጮሀል (ምክንያቱም ይህ የጋራ ወዳጃችን የቴሌ ሠራተኛ ነውና) 

‹‹...እውን እንዲህ አይነት ነገር አለ...... 500 ብሩን ልክፈል አልክፈል››  በማለት ይጠይቀዋል፡፡

በተጨማሪም ጉዳዩን በሠፊው ካብራራለት ቡሀላ ቁጥሩን ሠጥቶት ይሰናበታል፡፡ የቴሌው ወዳጃችን ጉዳዩ ስላስገረመው ኮምፒውተሩን ከፍቶ የቁጥሩን ባለቤት ተመለከተው፣ በግለሰብ ስም ነው የተመዘገበው፡፡ የደወለባቸውን የስልክ ቁጥሮች ዝርዝር ያወጣለት ዘንድ የሚጠይቀውን ሳጥን ሲጫን 0920 የሚሉ ቁጥሮችን ብቻ ነው የሚደውለው፡፡ ቅድም ሲመለከት የነበረበት 74 ብር 369 ብር ሆኖ ሲያየው ጭራሽ የማወቅ ፍላጎቱ ጨመረ፡፡ አሁንም ሳያመነታ ከደወለላቸው ሰዎች ዝርዝር አራቱን በመምረጥ ደወለላቸው፡፡

‹‹ከቴሌ ነው እንዲህ እነዲያ……….  የሚል ሠው ደውሎ ነበር›››

ከወድያ ‹‹ አዎን በእናትህ እስከዛሬ እየተበደርኩ በተለያየ ግዜ አንዴ ዳታቤዝ አንዴ አካውንትህ ጠፋብን ምናምን እያለኝ  400 (አራት መቶ ብር) ከላኩለት ቡሀላ ………››፡፡ 

የሚቀጥለውም ጋር ደወለ ሴት ነበር ያነሳችው ‹‹500 ብር ልኬለታለሁ ግን እስካሀን ምንመ ብር አላከልኝም››፡፡ 

ሶስተኛው ጋር ደወለ ‹‹ አዎ ደውሎ ነበር ግን ሰምቼ ብቻ ነው ዝም ያልኩት›› ፡፡

የመጨረሻው ጋር ደወለ ‹‹……. 500 ብር ተበላሁኝ ማለት ነው…›› በሚል የቁጭት ጥያቄ አዘል መሳይ መልሱን ሠጠው፡፡

ነገሩ ይበልጥ ሲያስገርመው እና ድፍረቱ ሲያስደንቀው፣ ቀጥታ ወደተባለው አስገራሚ የኤፍ.ኤም ጣቢያ ስልክ ቁጥርን ከኮምፒውተሩ እያመሳከር እፍለፊቱ ካለው የቢሮው ስልክ ላይ……

 ጠቅ ……. ጠቅ …….ጠቅ አድርጎ መነጋገርያውን ወደ ጆሮ አስጠጋ

ከወድያ ይጠራል ……. ጡጥ ……. ጡጥ …….

አኒቲ ነኝ

ይቀጥላል!

Comments

Popular posts from this blog

The Historic Chaltu Speeks Out

Let me paint you the picture of what happened in ATL yesterday. Me and Riyad S abona walking, minding our own business and we see an anti-Jawar protest happening 200 yards away from the meeting entrance. The police directed us to walk in closer to the side of the protest to avoid obstructing traffic.  So we saw their flags and I decided to take out my Oromo flag and walk.  First, it was just the slurs, calling me Galla. Then it was the spit, in front and behind me and then one made it with the perfect aim to hit my cheek. I continued to walk with my head high with the utmost respect until one 'balance' thought it would be okay to reach over and snatch my flag. He thought he got the flag, but I killed that dream, but as soon as he reached again and grabbed my hijab, I turned around and his face hit the back of my hand (like how words can change everything?). Lol, I actually slapped the hell out of him. When I looked back they were grabbing on Riyad's trad...

ከዶ/ር መረራ አስለቃሽ ጭስ አንዷ

ዶር መረራ ጉዲናን ሁላችንም እንደምናውቃቸው፣ በሀገራችን የመማር ማስተማር እና የፖለቲካ ምህዳር እንደ አስተማሪም እንደ አማራሪም በመሆን ከፍተኛ ሚና የተጫወቱና አንቱታን ያተረፉ የሀገራችን ዜጋ ናቸው።  አንደበተ ርቱ ባይባሉም መናገር የፈለጉትን ነገር ከመናገር ወደኋላ የማይሉ፣ ንግግራቸው ግልፅ እና ግልብ ከሚባል ተርታ ይመደባል ባይ ነኝ። እሳቸው ተናግረው አልያም ተከራክረው ፈገግ ያላልኩበት አጋጣሚ ትዝ አይለኝም። ከሰሞኑን የመታሰራቸውን ነገር በሰማሁ ወቅት፣ አንደ ወዳጄ አቀልድ ማህደሩ ይሁን አዚዓ ማህደር እነወጃ፣ አሉ ብሎ ካካፈለኝ ፈገግ የምታሰኝ ንግግራቸውን ላካፍላቹ ወደድኩ። ነገሩ የሆነው ፓርላማ ሳሉ ነው አሉ። የወቅቱ አፈጉባኤ ደግሞ ክቡር አቶ ተሸመ ቶጋ ነበሩ። አናም የመናገር እድሉ ሲደርሳቸው አቶ ተሾመ፣ ባላቸው ማይኩን የመዝጋትና የመክፈት ስልጣን፣ ቀጥል ብለዉት ደር መራራን እንዲናገሩ ፈቀዱላቸው። እናሎ ታድያ ወቅቱ የፓርላማው አመታዊ ሪፖርት በጠቅላይ ሚንስትሩ የሚቀርብበት ነበር፣ እንደሚታወቀው ዶር መረራ ቡዙን ግዜ ፓርላማ ላይ የማይቀሩበት አጋጣሚ ይህ እንደሆነ ይታወሳል። ይህንንም አጋጣሚ በመጠቀም (ቢቆራረጥም) ሚዲያውን በአግባቡ ይጠቀማሉ። ዶር መረራ ጀመሩ ፦ "ሲለ ተሰጠኝ እድል ባመሰጊን፣ ‘ፉት ሲሏት ጭልጥ’ እንደሚለው ተረት ቲሆናለች እና የተሰጠን ሰዐት ኢሀዴግ…" ብለው ሳይጨርሱ፣ አፈጉናኤው እላያቸው ላይ ማይኩን ጥርቅም አድርጉት። አፈ ጉባኤው:– "ደ/ር መረራ ሌላ ሌላውን ይተውና አጊባብነት የለው ጥያቄ ያቅርቡ፣ ጥያቄዎት ወይም አስታየቶ ክብር ሚኒስትሩ ባቀረቡት ሪፖርት ላይ ብቻ ይሁን፣ ከተሰጦት ሰዓት 5 ደቂቃ ብቻ ይቀሮታል" ቁጣን ባለው ለዛ ብለው  እንዳበቁ...

የድንቅነሽ/ሉሲ በደህና የመመለሷ ነገር . . .

ዛሬ ድንገት ኢቲቪ ተከፍቶ ዜና ሠማሁኝ እና ከዜናው አንዱ ትኩረቴን ሳብ አድርጎት ጆሮዬን ቀልቤን አቅሌን ሙሉ ለሙሉ ለኢቲቪ ሰጠሁ፡፡ ታድያሎ ያልኳችሁ ዜና እናንተም የሰማችሁት ያ ስለ ድንቅነሽ /ሉሲ/ ከ5 ዓመት ቆይታ ቡሀላ ከወደ አሜሪካን ሀገር ተመለሰች የሚለው ነበር፡፡ ገና የዜናው ርዕስ እንደሰማሁኝ ነበር፤ እንኳን በደህና ሄደሽ ባልልም፤ እንኳን ደህና መጣሽ ማለቴ ግድ ነበር፤   እናም አልኩኝ፡፡ ሙሉ የዜናውን ሀተታ እና የምስል ቅንብር ስመለከት፤ለርክክቡም አሜሪካዊ እና ታዋቂ ብሎም አዋቂ የኢትዮጰያዊ ተመራማሪዎች ከአሜሪካን ድረስ እዚህ መገኘታቸውን ሠማሁ፡፡ ከዛማ እንኳን በደህና ተመለስሽ ያልኩት አባባል ግልፅነት እና ተጠያቂነት የጎደለው ደብዛዛ ምስክርነት መስሎ ታየኝ፤ ጥርጣሬም ወረረኝ፡፡ ለምን እና እንዴት ካላችሁ. . . . . የ እኛ ምሁራን ሉሲን ገቢ ያደረጉበት የማረጋገጫ መለኪያ ተጠቀምን ያሉት ስልት እንደ ስለት አሳቀቀኝ፡፡ ፕሮፌሰሩ ቃል ሲሰጡ፤ “እያንዳንዷን አጥንት መዝነን፣ ለክተን ነው የተቀበልነው::” በዜናው ላይ የቀረበው የ ርክክብ ቪዲዮ ላይ እንዳየነው፤  እና መገለጫችን የሆነውን የሉሲን አፅም ለዛውም ለ5 ዓመት ያህል ሠው ቤት ቆይቶ እንደሚመለስ ብርቅዬ ቁስ ሳይሆን እንደ አሞሌ ሲቀባበሉ መመልከቴ አስገርሞኛል፡፡ በተለይ በተለይ የእኛው ምሁራን ይህችን በስንት ምርምር የእድሜ ጠገብነቷን ሚስጢር በዓለም አቀፍ ደረጃ ለመለየት ብዙ ምርምር የተደረገላትን በክብደት እና ቁመት በመለካት ማረጋገጥ ችለናል ማለታቸው አግራሞት ፈጥሮብኛል፡፡ እኔ የምለው እንደው ደረጃ መዳቢዎች ባለስልጣን እራሱ ዘይትን ከውጪ ለማስገባት ምን ያህል የላብራቶሪ ፍተሸ እናደሚያካሂድ ባለፈው ዘይት እንትን ያ...